የኢትዮጵያ እና የጀርመን ወታደራዊ ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ጉብኝት በሁርሶ ኮንቲጀት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ተካሄደ፡፡

259

ባሕር ዳር፡ ኅዳር 03/2013 ዓ.ም (አብመድ) የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የስላም ማሰከበር ማሰልጠኛ ተቋም አዛዥ ተወካይ ኮሎኔል ታምራት አንዳርጌ እንደተናገሩት የጉብኝቱ ትኩረት አዲስ የትራንስፖርት እና የጥገና ስራዎችን ለማቋቋም ፣ ማሰልጠኛውን ዘመናዊነቱን ጠብቆ ለማደስ እና አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ነው ብለዋል፡፡

የጀርመን ወታደራዊ አታሼ ኮሎኔል ቶማስ ሪበርሊንገ በበኩላቸው ባደረግነው የመስክ ጉብኝት ቀጣይ ላቀድነው እና ለምንሰራቸው ስራዎቻችን ምቹ ሁኔታ ይፈጥርልናል፤የጀርመን እና የኢትዮጵያ ወታደራዊ ትብብርም ተጠናክሮ ይቀጥላል ማለታቸውን የሃገር መከላከያ ሚኒስቴር በይፋዊ ገፁ አስነብቧል፡፡

Previous articleከሃዲውን የህወሃት ቡድን የሚያወግዝ ሰልፍ በሀዋሳ እየተካሄደ ነው፡፡
Next articleከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ የተላለፈ መልዕክት