ከሃዲውን የህወሃት ቡድን የሚያወግዝ ሰልፍ በሀዋሳ እየተካሄደ ነው፡፡

238

ባሕር ዳር፡ ኅዳር 03/2013 ዓ.ም (አብመድ) ከሀዲው የህወሃት ቡድን በመከላከያ ሰራዊት ላይ የወሰደውን ጥቃት የሚያወግዝ ሰልፍ በሀዋሳ እየተካሄደ ነው።

በሰላማዊ ሰልፉ ከሲዳማ ክልል ሁሉም ወረዳዎች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

ሰልፈኞቹ ከሃዲው የህወሃት ጁንታ ቡድን በመከላከያ ሰራዊት ላይ ያደረሰውን ጥቃት የሚቃወሙ መፈክሮችን በመያዝ እያወገዙ ነው።

ከመፈክሮቻቸው መካከልም ‹‹በመከላከያ ሰራዊታችን ላይ ከሃዲው ጁንታ የህወሃት ቡድን የወሰደውን እርምጃ እንቃወማለን፤ከመከላከያ ሰራዊታችን ጎን ሆነን የሚጠበቅብንን ድጋፍ ሁሉ እናደርለን››የሚሉ እና ሌሎች መፈክሮችን አሰምተዋል።

ሰልፈኞቹ ለመከላከያ ሰራዊቱ ያላቸውን አጋርነትም በመግለጽ ላይ መሆናቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous article“የሕወሃት ወንጀለኞች በአዲስ አበባ እና በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ፍርሃትን ለመንዛትና እና የሽብር ጥቃትን ለማድረስ አስፈፃሚ መረብ አቋቁመዋል” የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ
Next articleየኢትዮጵያ እና የጀርመን ወታደራዊ ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ጉብኝት በሁርሶ ኮንቲጀት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ተካሄደ፡፡