“የሕወሃት ወንጀለኞች በአዲስ አበባ እና በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ፍርሃትን ለመንዛትና እና የሽብር ጥቃትን ለማድረስ አስፈፃሚ መረብ አቋቁመዋል” የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ

192

ባሕር ዳር፡ ህዳር 03/2013 ዓ.ም (አብመድ) ግጭቶችን በማነሳሳት እና በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሽብር ጥቃቶችን በማካሄድ ተልዕኮ በሕወሃት ተላላኪነት የተጠረጠሩ ግለሰቦች በፌደራል እና በአዲስ አበባ ፖሊስ በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ከተለያዩ የኑሮ ዘርፎች የተውጣጡ የተለያዩ ብሔር ተወላጆች ናቸው ፡፡ በቁጥጥር ስር የዋሉት ተጠርጣሪዎች ጠቅላላ ቁጥር ወደ 150 አካባቢ ነው፡፡ ከነዚህ ተጠርጣሪዎች መካከል ጥቂቶቹ በዋስ ተለቀዋል፡፡

እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ ብዙ ድርጅቶች እና ግለሰቦች በተሳሳተ መንገድ የእስረኞችን ቁጥር በተመለከተ ሙሉ በሙሉ ያልተረጋገጠ እና የተጋነነ መረጃ እያሰራጩ ይገኛሉ፡፡ የሕግ አስከባሪያችን አሠራር ደንብን የተከተለ እንጂ እንደሚወራው በማንነት ላይ ተመስርቶ ግለሰቦችን የሚያጠቃ አይደለም፡፡

ሁሉም ዓለም አቀፍ አጋሮች እና ተዋንያን በሕወሃት እየተፈፀመ ያለውን የውሸት መረጃ ዘመቻ ልብ እንዲሉ ጥሪ እናቀርባለን ብሏል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleበህገወጡ የትህነግ ቡድን ላይ ህግ የማስከበር ርምጃ እየፈፀሙ ለሚገኙት ለሃገር መከላከያ ሰራዊት፣ ለአማራ ክልል ልዩ ኃይል እና ለሚሊሻ አባላት የሚደገው ድጋፍ እንደቀጠለ ነው፡፡
Next articleከሃዲውን የህወሃት ቡድን የሚያወግዝ ሰልፍ በሀዋሳ እየተካሄደ ነው፡፡