የህወሃት ጁንታ የኤርትራ መከላከያ ሰራዊትን መለዮ ለታጣቂዎች በማልበስ ኤርትራ እንደወረረችው በመግለጽ ሕዝብን እያደናገረ መሆኑን መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።

1296

ባሕር ዳር፡ ኅዳር 02/2013 ዓ.ም (አብመድ) “ሁመራና አካባቢው ሙሉ ለሙሉ በመከላከያ ሰራዊት ቁጥጥር ስር ውሏል” ሲሉ የአገር መከላከያ ሰራዊት የኢንዶክትሪኔሽን ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል መሐመድ ተሰማ ተናግረዋል፡፡

ሰራዊቱ በአሁኑ ወቅት ከሁመራ እስከ ሽራሮ ያለውን ቦታ በማጥቃት የተለያዩ ስፍራዎችን በቁጥጥር ስር እያዋለ እንደሚገኝም አመልክተዋል።

ሰራዊቱ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ለሚኖሩ ሰዎች ድጋፍ ማድረግ የሚፈልጉ የእርዳታ ድርጅቶች ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር ተነጋግረው ድጋፍ ማድረግ እንደሚችሉም ጠቁመዋል።

የህወሃት ጁንታ በአልመዳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ የኤርትራ መከላከያ ሰራዊትን መለዮ በማዘጋጀት ላደራጃቸው ታጣቂዎች በማልበስ ኤርትራ እንደወረረች በመግለጽ ሕዝብን እያደናገረ እንደሆነም አስታውቀዋል።

በዚህ የተቀናበረ ድራማ ሕዝቡ ሳይታለል ለመከላከያ ሰራዊቱ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ማቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

Previous articleየኢፌዴሪ አየር ሀይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጄነራል ይልማ መርዳሳ አየር ኃይል ጠላት ሊጠቀምባቸው ያሰባቸውን ኢላማዎች በመደብደብ ከጥቅም ውጭ ማድረጉን አስታወቁ።
Next articleበህገወጡ የትህነግ ቡድን ላይ ህግ የማስከበር ርምጃ እየፈፀሙ ለሚገኙት ለሃገር መከላከያ ሰራዊት፣ ለአማራ ክልል ልዩ ኃይል እና ለሚሊሻ አባላት የሚደገው ድጋፍ እንደቀጠለ ነው፡፡