የኢፌዴሪ አየር ሀይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጄነራል ይልማ መርዳሳ አየር ኃይል ጠላት ሊጠቀምባቸው ያሰባቸውን ኢላማዎች በመደብደብ ከጥቅም ውጭ ማድረጉን አስታወቁ።

1156

ባሕር ዳር፡ ኅዳር 02/2013 ዓ.ም (አብመድ) ለጁንታው እስትንፋስ የነበሩ የነዳጅ ዴፖዎች ፣ የመሳሪያ ማከማቻዎች እና ሌሎች ምርጥ ኢላማዎች የኢትዮጵያ አየር ኃይል ጀቶች ያለምንም ከልካይ እንዳሻቸው እየተመላለሱ አውድመዋቸዋል ብለዋል።

የአየር ኃይል አብራሪዎች የተመረጡ ዒላማዎችን ለመደምሰስ መሣሪያ ጭነው እየሄዱ ሲቪል የሚጎዳ ከመሰላቸው ሳይተኩሱ በመመለስ ነጥሎ የመምታት ስትራቴጂ እየተከተሉ እንደሚገኙም አስገንዝበዋል።

“ጁንታው ጄቶችን እንመታለን የሚለው እድሜውን ሲዋሽ ስለኖረና እየዋሸ ስለሚቀበር ነው፤ በተፈለገ ሰዓት እየተመላለስን ጁንታው ለህግ እስኪሚቀርብ ድረስ ማጥቃታችንን እንቀጥላለን” ማለታቸውን የሃገር መከላከያ ሚኒስቴር በይፋዊ ገፁ አመላክቷል።

Previous articleኢትዮጵያ በትግራይ የምታካሂደው ህግን የማስከበር ዘመቻ የውጭ ጣልቃ ገብነት እንደማያስፈልገው በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ሆነው የተሾሙት ዣኦ ዢዩአን አረጋገጡ።
Next articleየህወሃት ጁንታ የኤርትራ መከላከያ ሰራዊትን መለዮ ለታጣቂዎች በማልበስ ኤርትራ እንደወረረችው በመግለጽ ሕዝብን እያደናገረ መሆኑን መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።