የትህነግ ጁንታ ቡድን በመጥፊያው መጨረሻ ሰዓት ላይ ሆኖ የሀሰት ፕሮፓጋንዳ እየነዛ መሆኑን መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

561

ባሕር ዳር፡ ህዳር 02/2013 ዓ.ም (አብመድ) የመከላከያ ሚኒስትሩ ቀንአ ያደታ (ዶክተር) በሰጡት መግለጫ በትግራይ ክልል ህግ የማስከበር ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡ ይህ የተደራጀ ጁንታ የሀገር መከላከያን በማጥቃት ሃገርን የማፍረስ እና ሉዓላዊነቷ ላይ አደጋ የጣለ ቡድን መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ነገር ግን የጥፋት ቡድኑ በሀሰተኛ መረጃ ሕዝብን ማደናገር መጀመሩ ተስፋ እየቆረጠ ለመምጣቱ ማሳያ እንደሆነ ነው የመከላከያ ሚኒስቴሩ ያስታወቁት፡፡

ቡድኑ ህግ የማስከበር ስራውን የእርስ በእርስ ጦርነት ለማስመሰል በርካታ የተሳሳቱ መረጃዎችን ይፋ እያደረገ እንደሚገኝም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።

የትህነግ ቡድን ውሸት ተፈጥሯዊ ስሪቱ መሆኑን ዶክተር ቀንዓ ገልጸዋል። አሁን ላይ በጥፋት ቡድኑ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቅሰዋል።

የትግራይ ልዩ ሀይልና ሚሊሻ አባላት የዚህ ቡድን ከለላ ከመሆን ይልቅ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት እጃቸውን እንዲሰጡ፣ ካልሆነ ግን መከላከያው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ለመደምሰስ እንደሚገደድ የመከላከያ ሚኒስቴሩ አስታውቀዋል።

ዘጋቢ፡ – አንዷለም መናን ከአዲስ አበባ

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleየሃገር መከላከያ ሰራዊቱ የማንንም የውጭ ሃይል ድጋፍ ሳይፈልግ የጥፋት ቡድኑን የመደምሰስ ቁመና ላይ መሆኑን የመከላከያ ሚኒስትር ዶክተር ቀንዓ ያደታ ገለጹ።
Next articleህገ ወጡ የትህነግ መንግሥት እየፈጸመው ያለውን ግፍ ለመላው ዓለም ለማሳወቅ በአማራ ክልል ህዝባዊ የሰላማዊ ሰልፍ በነገው እለት ይካሄዳል፡፡