የሃገር መከላከያ ሰራዊቱ የማንንም የውጭ ሃይል ድጋፍ ሳይፈልግ የጥፋት ቡድኑን የመደምሰስ ቁመና ላይ መሆኑን የመከላከያ ሚኒስትር ዶክተር ቀንዓ ያደታ ገለጹ።

349

ባሕር ዳር፡ ኅዳር 02/2013 ዓ.ም (አብመድ) የመከላከያ ሚኒስትሩ በሃገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ መግለጫ እየሰጡ ነው።

በመግለጫቸው እንዳመለከቱት የህወሃት የጥፋት ቡድንን ለመደምሰስ የማንንም የውጭ ሃይል ድጋፍ አይፈለግም ብለዋል።

የትግራይ ህዝብ የጥፋት ቡድኑን ሴራ በመገንዘብ ለጉዳት እንዳይዳረግም አሳስበዋል፡፡

ህዝቡ ለሰራዊቱ እያሳየ ያለውን ድጋፍ እንዲያጠናክርም ጥሪ አቅርበዋል።

የመከላከያ ሰራዊት በዘራፊው የህወሃት ቡድን ላይ በርካታ ድል እየተቀዳጀ እንደሚገኝ መግለፃቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

Previous articleየትህነግ ሰው በላ ቡድን በማይካድራ በንጹኀን ሰዎች ላይ ጭፍጨፋ ፈጽሟል።
Next articleየትህነግ ጁንታ ቡድን በመጥፊያው መጨረሻ ሰዓት ላይ ሆኖ የሀሰት ፕሮፓጋንዳ እየነዛ መሆኑን መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡