በትግራይ ክልል እየተከናወነ የሚገኘው ህግን የማስከበር ዘመቻ በታቀደው መንገድ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዐብይ አህመድ አስታወቁ፡፡

260

ባህር ዳር፡ ኅዳር 1/2013 ዓ.ም (አብመድ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በትዊተር ገጻቸው እንዳሉት በትግራይ ክልል ህግን የማስከበር ዘመቻው በተቀመጠው እቅድ መሰረት እየተከናወነ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዘመቻው በትህነግ ውስጥ ያለው ጁንታ ትጥቅ ሲፈታና በክልሉ ህጋዊ አስተዳደር ሲመለስ ዘመቻው እንደሚጠናቀቅም አስታውቀዋል፡፡

ህግ የማስከበሩ ርምጃም በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Previous articleዘንድሮ ለሚከበረው 15ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች በዓል የብሔር ብሔረሰቦች በዓል የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት ችቦ በዛሬው ዕለት በጅግጅጋ ከተማ ተለኩሷል።
Next articleህገወጡን የህወሃት ቡድንን ለመደምሰስ በግንባር እየታገሉ ለሚገኙ ለመከላከያ ሰራዊት፣ ለአማራ ክልል ልዩ ኃይል እና ሚሊሻ አባላት የሚውል የደም ልገሳ መርሃ ግብር በወልድያ ከተማ እየተከናወነ ነው፡፡