ዘራፊውን የህወሃት ቡድን ለመደምሰስ እየተወሰደ ባለው ርምጃ ለመከላከያ ሰራዊቱ፣ ለአማራ ልዩ ኃይል እና ለሌሎችም የፀጥታ አካላት የሚደረገው የቁሳቁስና የሞራል ድጋፍ ከተለያዩ አካባቢዎች ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው፡፡

322

ባሕር ዳር፡ ኅዳር 1/ 2013 ዓ.ም (አብመድ) በወልቃይት ከተማ ንጉስ እና አካባቢው ለሚገኘው የመከላከያ ሰራዊትና የፀጥታ አካላት ከደምቢያ፣ ላይ አርማጭሆ፣ አይከል ከተማ ጭልጋ ቁጥር አንድ እንዲሁም ከሌሎች በርካታ ወረዳዎች የሰንጋ፣ የበግ እና ፍየል፣ የምግብ እህል ብሎም ዉኃ ድጋፍ ሲደረግ የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት በቦታው ተገኝቶ ተመልክቷል፡፡

ከምዕራብ ደምቢያ ወረዳ አስተዳደር እና ከህዝቡ የተውጣጣ የበግ እና ፍየል እንዲሁም የምግብ እህል ይዘው ያገኘናቸው አስተባባሪ ኮሚቴዎች ዘራፊ ቡድኑን ለመዋጋት መሳሪያ ታጥቆ ግምባር ከመገኘት ባለፈ ይህንን አይነት ድጋፍ አጠናክሮ ማስቀጠል ተገቢ ነው ብለዋል፡፡

መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከሃዲውን እና ዘራፊውን የህወሃት ቡድንን እየተዋጋ ያለውን ሰራዊት በቁሳቁስ እና በሞራል ሊደግፍ እንደሚገባም አስተያየት ሰጭዎቹ ተናግረዋል፡፡

ዘጋቢ፡- አብዮት ከፋለ

Previous articleየትግራይ ህዝብ የትህነግ ዘራፊ ቡድንን የጥፋት ድርጊት በመቃወም ከሐገር መከላከያ ሰራዊት ጎን መቆም እንዳለበት በቆቦ ከተማ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ተናገሩ።
Next articleየትህነግ ቡድን በመከላከያ ሠራዊት ላይ የፈጸመውን ክህደት በጎንደር ከተማ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች አወገዙ፡፡ ነዋሪዎቹ በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው።