የትግራይ ህዝብ የትህነግ ዘራፊ ቡድንን የጥፋት ድርጊት በመቃወም ከሐገር መከላከያ ሰራዊት ጎን መቆም እንዳለበት በቆቦ ከተማ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ተናገሩ።

468

ባሕር ዳር፡ ኅዳር 1/ 2013 ዓ.ም (አብመድ) የአማራና የትግራይ ህዝብ በወንድማማችነትና በመተሳሰብ ለዘመናት የኖሩ እንደሆኑ ያነሱት የትግራይ ተወላጆች በቆቦ ከተማ ለረጅም አመታት ትዳር መስርተው ሐብት አፍተው እየኖሩ መሆኑን ለአብመድ ተናግረዋል።

ሽፍታው የትህነግ ጁንታ በሐገር መከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመው ጥቃት ቀድሞውንም ለህዝብና ለሐገር እንደማያስብ ያረጋገጠ ነው ብለዋል።

የትግራይ ህዝብ የከሐዲውን ቡድን እኩይ አላማ በማክሸፍ ህግና ስርዓትን ለማስከበር እየታገለ ካለው የሐገር መከላከያ ሰራዊት ጎን መሰለፍ አለባቸው ሲሉም በቆቦ ከተማ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች አሳስበዋል።

ህገወጡ ትህነግ እድሜያቸው ለውትድርና ያልደረሱ ህጻናት ጭምር ለጦርነት እያሰለፈ በመሆኑ የትግራይ ህዝብ ልጆቹን ከትህነግ እኩይ ድርጊት ሊታደጋቸው ይገባልም ብለዋል።

የትህነግን አፈናና እንግልት በመቃወምም ከአላማጣ ወረዳ ወደ ራያ ቆቦ ወረዳ የገቡ ነዋሪዎችም አሉ።

የማንነት ጥያቄያችን ይመለስ ብለን በተደጋጋሚ ስንጠይቅ ህገወጡ ትህነግ አፈና በማድረግ እያንገላታን በመሆኑና ከሰሞኑም በሀገር ላይ ክህደት በመፈጸሙ አካባቢውን ለቀን እንድንወጣ ምክንያት ሆኖናል ብለዋል።

ዘጋቢ፡- ስማቸው እሸቴ

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleበሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመው ጥቃት በወታደራዊ ሕግ የሚያስጠይቅ ከፍተኛ ወንጀል መሆኑን የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር ወለድ 102ኛ ክፍለ ጦር ገለጸ፡፡
Next articleዘራፊውን የህወሃት ቡድን ለመደምሰስ እየተወሰደ ባለው ርምጃ ለመከላከያ ሰራዊቱ፣ ለአማራ ልዩ ኃይል እና ለሌሎችም የፀጥታ አካላት የሚደረገው የቁሳቁስና የሞራል ድጋፍ ከተለያዩ አካባቢዎች ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው፡፡