በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመው ጥቃት በወታደራዊ ሕግ የሚያስጠይቅ ከፍተኛ ወንጀል መሆኑን የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር ወለድ 102ኛ ክፍለ ጦር ገለጸ፡፡

382

ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም (አብመድ) የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ወለድ 102ኛ ክፍለ ጦር በሰሜን ዕዝ ላይ የህገወጡ ትህነግ ልዩ ሃይል የፈጸመው ጥቃት በእጅጉ አሳፋሪ፣ ሃገራዊ ክህደትና በወታደራዊ ሕግ የሚያስጠይቅ ከፍተኛ ወንጀል መሆኑን ገልጿል።

ጦሩ በመግለጫው እንዳለው ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ነፃነታቸውን አስጠብቀው ከኖሩ ጥቂት ሃገራት አንዷና እንደነፃነት ቀንዲል የምትታይ የመላው ጥቁር ሕዝብ መመኪያ ናት፤ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሃገራትም ሆነ ከአውሮፓውያን በተለያየ ጊዜ የተቃጣባትን ጥቃት መክታ መመለስ ብቻ ሳይሆን የሌሎች ሃገራትን ሰላም ለማስጠበቅ በተለያዩ የዓለም ሃገራት ዘምቶ ታሪክ የሚያወሳው ጀብድ ፈጽሟል።

ከሰሞኑ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሰሜን ዕዝ ላይ የህገወጡ የትህነግ ልዩ ሃይል የፈጸመው ጥቃት በእጅጉ አሳፋሪ፣ ሃገራዊ ክህደትና በወታደራዊ ሕግ የሚያስጠይቅ ከፍተኛ ወንጀል ሆኖ አግኝተነዋል ብሏል፤ይህንን ከጀርባ የተፈጸመ አስነዋሪ ደባ የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ወለድ 102ኛ ክፍለ ጦር አባላት አምርረን እንደምናወግዘው እየገለጽን ትናንት ለሉዓላዊነቷ ለደማንላት ውድ ሃገራችን ዛሬም በግንባር ቀደምትነት እንደምንቆም ለመላው ሕዝባችን እንገልጻለን ሲል ማስታወቁን ኢዜአ ዘግቧል።

Previous articleህገወጡን የትህነግ ቡድን ለመመከት የትጥቅ እና የሥነ ልቦና ዝግጅት በማድረግ ወደ መከላከል ተግባር መግባታቸውን የሚሊሻ አባላት ተናገሩ፡፡
Next articleየትግራይ ህዝብ የትህነግ ዘራፊ ቡድንን የጥፋት ድርጊት በመቃወም ከሐገር መከላከያ ሰራዊት ጎን መቆም እንዳለበት በቆቦ ከተማ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ተናገሩ።