በሰሜን ኢትዮጵያ በመከላከያ ሰራዊት እየተወሰደ ያለው እርምጃ ግልጽ፣ የተወሰነ እና ሊደረስበት የሚችል አላማን ያነገበ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተናገሩ፡፡

399

ባሕር ዳር፡ጥቅምት 27/ 2013 ዓ.ም (አብመድ) ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለፈው ማክሰኞ ህወሓት ትግራይ ክልል በሚገኘው የሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ መከላከያ ሰራዊት እርምጃ መውሰድ መጀመሩን በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ አስታውቀዋል፡፡

እየተካሄደ ያለው ዘመቻም በሃገሪቱ ህግና ስርአትን ለማስፈን እና ህገ መንግስታዊ ስርአቱን ለማስከበር ያለመ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡ ህግና ስርዓት የማስከበሩ ተግባር በየትኛውም የሃገሪቱ አካባቢ ተንቀሳቅሰው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ደህንነት ለማስጠበቅ ያለመ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

መንግስት ከህወሓት ጋር ያለውን ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ለወራት ታግሶ ድርድርና ሽምግልና ሲያካሂድ መቆየቱንም አስታውሰዋል፡፡ ሆኖም መንግስት ያደረገው ጥረት በሙሉ በህወሃት እምቢተኝነት መክሸፉንም አስታውቀዋል፡፡

Previous articleየሕዝብ ሠላምን በአስተማማኝ መልኩ ማስቀጠል የሚያስችል አደረጃጀት መፍጠሩን የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር አስታወቀ፤ በዞኑ የጸጥታ ችግር የስጋት ቀጣና በተባሉ አካባቢዎች ጠንካራ አመራር እየተሠጠ መሆኑን የዞኑ የሕዝብ ሠላምና ደኅነት መምሪያ ገልጿል፡፡
Next article“ለኛ መኖር መስዋዕትነት እየከፈሉ ላሉ ወገኖቻችን ደም ለግሰን ህይወታቸውን እናስቀጥል” በሚል መሪ መልዕክት የገንዳ ውሃ ከተማ ነዋሪዎች ደም እየለገሱ ነው።