በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ ዋጋ ቃንቃ ቀበሌ በንፁሀን ዜጐች ላይ በደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የፌዴሬሽን ምክር ቤት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጿል፡፡

253

ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም (አብመድ) የፌዴሬሽን ምክር ቤት እንደገለጸው በንፁሀን ዜጐች ላይ እየደረሰ ያለው አሰቃቂ ጥቃት በተደጋጋሚ እየተፈፀመ የዜጐችን ህይወት እየቀጠፈም ይገኛል፤ በመሆኑም ለሀገርና ለሰው ልጅ ክብርና ስብዕና በሌላቸው የጥፋት ሃይሎች ላይ መንግስት የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥ አለብት ብሏል፡፡

የሃገሪቱ ብሄሮች ፣ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች መንግስት በነዚህ የጥፋት ኃይሎችና አሸባሪዎች ላይ ለሚወስደው እርምጃ ከመንግስት ጐን በመቆም አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ነው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ጥሪውን ያቀረበው፡፡

ምክር ቤቱ ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን የገለፀ ሲሆን ለተጎጂ ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች እንዲሁም ለመላው ኢትዮጵያውያን መጽናናትን እንደሚመኝ ገልጿል፡፡

Previous article“ዘር ተኮር ጥቃቱ ያስተማረን እውነት ቢኖር የለውጥ ሃይሉን ሃሳብ ከልብ የሚደግፉት ውስኖች ብቻ እንደሆኑ ነው” ምሁራን
Next article”ሰላማዊ ሕዝብን በመጨፍጨፍና በማስጨፍጨፍ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚንቀሳቀሱ ቡድኖች ሰው የመሆን ስብዕና የጎደላቸው ናቸው” አቶ ኡሞድ ኡጁሉ