በኢትዮጵያ እየተስተዋለ ያለውን ግጭት ለማስወገድ በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አሳሰበ፡፡

313

ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 12/2013 (አብመድ) በኢትዮጵያ የሚታየውን ግጭት እና አለመረጋጋት ለማስወገድ የሃይማኖት መሪዎች፣ መንግሥት እና ምዕመናን ትኩረት ሰጥተው ሊሠሩ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አሳስቧል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የቅዱስ ሲኖዶሱን ጉባኤ ሲከፍቱ እንዳሉት በኢትዮጵያ እየተስተዋሉ ያሉት ግጭቶችና አለመግባባቶች ብዙ ጉዳቶችን እያስከተሉ ነው፡፡

ልዩነቶችን በውይይት በመፍታት እርቅን ማስፈን እና ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥ እንደሚገባ ፓትርያርኩ አሳስበዋል፡፡

ቤተ ክርስቲያኗ የአክራሪዎች፣ የተቃራኒዎች እንቅስቃሴ እንዲሁም ውስጣዊ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እየገጠሟት መሆኑን ተናግረው ጉባኤው እነዚህን ችግሮች ለመፍታት በንቃት እንዲሠራ አቡነ ማትያስ ማሳሰባቸውን ኢብኮ ዘግቧል፡፡

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleየታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አጭር የጽሁፍ መልዕክት የገቢ ማሰባሰቢያ 3ኛ ዙር ሁለተኛ ተሸላሚ መኪናቸውን ተረክበዋል፡፡
Next articleየኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በሥስት ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ፡፡