የዓለም ጤና ድርጅት ለኮሮናቫይረስ የተዘጋጀው ሬምዴስቬር መድኃኒት ላይ ሙከራ አካሂዷል። ድርጀቱ በሙከራው መድኃኒቱ የሞት ምጣኔን በመቀነስ በኩል የሚጫወተው ሚና አነስተኛ መሆኑንም ተናግሯል፡፡

219

ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 06/2013 ዓ.ም (አብመድ) የዓለም ጤና ድርጅት ፀረ- ቫይረስ መድኃኒት የተባለውን ሬምዴስቬርን ጨምሮ በአራት መድኃኒቶች ላይ ሙከራ አካሂዷል፡፡ መድኃኒቱ ታካሚዎች በሕክምና ተቋማት ውስጥ የሚያሳልፉትን ጊዜ በማሳጠርም ሆነ በሕይወት እንዲቆዩ የሚያበረክቱት አስተዋፅዖ ዝቅተኛ ነው፡፡

ሙከራው ከተደረገባቸው ዉስጥ ሬምዴስቬር፣ ሀይድሮክክሎሮኪን፣ ሎፒናቪርና ኢንተርፌሮን ናቸው፡፡ በሙከራ የተገነው ውጤት በጤናው መስክ ላይ በተሰማሩ ባለሙያዎች የሚገመገም ይሆናል፡፡

በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪ ጁሊ ፊሸር (ተባባሪ ፕሮፌሰር) ለአልጀዚራ እንደተናገሩት የሙከራው ውጤት የሚያበሳጭ ነው፡፡ ሙከራው የሬምዴስቬር ጠቀሜታን በዝርዝር ያላስቀመጠ ነው ብለዋል፡፡

ሬምዴስቬር በኢቦላ ቫይረስ ለተያዙ ሰዎች ተሻሽሎ የተዘጋጀ መድኃኒት ነው፡፡ በአሜሪካው መድኃኒት አምራች ኩባንያ ጊሊያድ የቀረበ ነው፡፡

በኮሮና ቫይረስ ለሚሰቃዩ ሰዎች ሕክምና ለመስጠት ያገለግላል ተብሎ በግንባር ቀደምትነት ጥቅም ላይም ውሏል፡፡ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኮሮና ቫይረስ በተያዙበት ወቅት ይህን መድኃኒት መውሰዳቸውም የሚታወስ ነው፡፡

በኪሩቤል ተሾመ

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleአዲሱ የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ድረስ ሳኅሉ (ዶክተር) ማናቸው?
Next articleየደረሱ ሰብሎችን በመሰብሰብ የአንበጣ መንጋን ለመከላከል ሁሉም ኅብረተሰብ እንዲረባረብ የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር ጥሪ አቀረበ፡፡