አዲሱ የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ድረስ ሳኅሉ (ዶክተር) ማናቸው?

467

ዶክተር ድረስ ሳኀሉ ጎሹ የትምህርት ዝግጅታቸው
• በዲፕሎማ በደን ሳይንስ ከወንዶ ገነት የደን ሳይንስ ኮሌጅ
• የመጀመሪያ ዲግሪ በመልክዓምድርና አካባቢ ጥናት ከሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ
• የሁለተኛ ዲግሪ በመልካም አስተዳደርና በአመራር ጥበብ ከኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ
• የሦስተኛ ዲግሪያቸውን በሥራ አመራር ፍልስፍና ቻይና ሀገር ከሚገኘው ኋጁንግ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል፡፡ ዶክተር ድረስ ሳኀሉ ሁሉንም የትምህርት ደረጃዎች በከፍተኛ ማዕረግ ያጠናቀቁ መሆናቸውን ታሪካቸው ያስረዳል፡፡

ዶክተር ድረስ ሳኀሉ በሥራ ልምድ በኩል ደግሞ
• በምስራቅ ጎጃም ዞን በደባይ ጥላት ግን እና በባሶ ሊበን ወረዳ የደን አግሮ ፎረስተሪና የመሬት አስተዳደር ባለሙያ በመሆን ለአራት ዓመታት አገልግለዋል፡፡
• በምስራቅ ጎጃም ዞን በባሶ ሊበን ወረዳ የአስተዳደር እና ግብርና ጽኅፈት ቤት ኃላፊ በመሆን
• በአነደድ ወረዳ የግብርና ኃላፊ፣ የመሬት አስተዳደር ጽኅፈት ቤት ኃላፊ፣ የሕዝብ ተሣትፎና አደረጃጃት አማካሪ በመሆን አገልግለዋል፡፡
• በምዕራብ ጎጃም ዞን ቋሪት ወረዳ ምክትል አስተዳደሪና ግብርና ጽኅፈት ቤት ኃላፊ
• በጃቢ ጠህናን ወረዳ የመሬት አስተዳደር ጽኅፈት ቤት ኃላፊና የሕዝብ ግንኙነት አማካሪ በመሆን አገልግለዋል፡፡
• የምዕራብ ጎጃም ዞን ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ፣ የሕዝብ ግንኙነትና የከተማ አደረጃት አማካሪ
• በአማራ ክልል የምሁራን ተሳትፎና አደረጃጀት ዘርፍ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል፡፡

በታርቆ ክንዴ

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleከተማ አስተዳደሩ በፕላንና በህጋዊ የከተማ እድገት አቅጣጫ ብቻ እንድትማራ አጥብቀው እንደሚሰሩ ዶክተር ድረስ ሳህሉ ተናገሩ።
Next articleየዓለም ጤና ድርጅት ለኮሮናቫይረስ የተዘጋጀው ሬምዴስቬር መድኃኒት ላይ ሙከራ አካሂዷል። ድርጀቱ በሙከራው መድኃኒቱ የሞት ምጣኔን በመቀነስ በኩል የሚጫወተው ሚና አነስተኛ መሆኑንም ተናግሯል፡፡