
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 06/2013 ዓ.ም (አብመድ) ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶክተር) ከአማራና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች መሪዎች ጋር ተወያይተዋል።
ከአማራ እና ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ የክልል መሥተዳድሮች እንዲሁም ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በመተከል ዞን የተፈጸሙ ጥቃቶችን አስመልክቶ ነው የተወያዩት። “ያሉትን ችግሮች ፈትሸን፣ የአካባቢውን ዘላቂ ሰላም ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠናል” ብለዋል ጠቅላይ ሚንስትሩ በማኀበራዊ ገጻቸው::
