ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በዚህ ሳምንት የተመረቀውን የእንጦጦ ፓርክን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ጋር እየጎበኙ ነው፡፡

421
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 04/2013ዓ.ም (አብመድ) ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ እያደረጉት ባለው ሦስተኛ ቀን የሥራ ጉብኝት በጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ አስጎብኝነት የእንጦጦ ፓርክን በመጎብኘት ላይ ናቸው።
 
 
ኢብኮ እንደዘገበው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በዚህ ሳምንት የተመረቀውን የእንጦጦ ፓርክን ፕሮጀክቱ ከመጀመሩ በፊት፣ ፕሮጀክቱ በመሠራት ላይ እያለ እና የአሁኑን የተጠናቀቀውን የፓርክ ጉብኝት ጨምሮ ለሦስት ጊዜ ጎብኝተውታል።
 
 
የእንጦጦ ፓርክ ለአንድ ዓመት ያህል ግንባታው ሲካሄድ ቆይቶ መስከረም 30 ቀን 2013ዓ.ም በጠቅላይ ሚነስትር ዐብይ አህመድ ተመርቆ ለሕዝብ ክፍት መደረጉ ይታወሳል።
ሁለቱ መሪዎች ባለፉት ሁለት ቀናትም የኮይሻ እና የታላቁ ሕዳሴ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።
Previous article“የመከራዎቻችን ወቅት ነጋዴዎች እና የክፉ ቀኖቻችን አትራፊዎች ከድርጊታቸው ሊታቀቡ ይገባል፡፡” የደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደር
Next articleከጎጃም መስመር ወደ ወደ አዲስ አበባ የሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ጥቃት እየተፈጸመባቸው መሆኑን ተናገሩ፡፡