ክርስቲያኖ ሮናልዶ የኮሮናቫይረስ ተገኘበት፡፡

802

ፖርቱጋላዊው የእግር ኳስ ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በኮሮናቫይረስ መያዙን የሀገሪቱ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡

የጁቬንቱስና ፖርቱጋል አጥቂው በኮሮናቫይረስ መያዙንና የሕመም ምልክቶች ግን እንዳልታዩበት የፖርቱጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽንን ጠቅሶ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ባለፈው እሑድ በአውሮፓ ሀገራት ዋንጫ ማጣሪያ ከፈረንሳይ ያለግብ አቻ የተለያየችው ፖርቱጋል የፊታችን ረቡዕ ከስዊድን ጋር ለሚኖራት ጨዋታ የኮከቧን ግልጋሎት እንደማታገኝ ታውቋል፡፡

Previous articleመንግሥት አፋጣኝ ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ሰብላቸው በበርሃ አንበጣ መንጋ የወደመባቸው የባቲ ወረዳ አርሶ አደሮች ጠየቁ፡፡
Next articleመንግሥት አፋጣኝ ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ሰብላቸው በበርሃ አንበጣ መንጋ የወደመባቸው የባቲ ወረዳ አርሶ አደሮች ጠየቁ፡፡