ሶማሊያዊው ዳኛ ዑመር አርታን በአውሮፓ ሱፐር ካፕ ታሪክ ሊሠሩ ነው።

0
54
ሶማሊያዊው የመሐል ዳኛ ዑመር አርታን ፓሪስ ሴንት ዠርሜን ከአስቶን ቪላ የሚያደርጉትን የአውሮፓ ሱፐር ካፕ ዋንጫ ጨዋታን በመምራት የመጀመሪያው አውሮፓዊ ያልኾኑ ዳኛ በመኾን አዲስ ታሪክ ሊጽፉ ነው።
ዳኛው ቀደም ሲል ለ2026 የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ለመዳኘት ወደ አሜሪካ ለመግባት ያቀረቡት የመግቢያ ፈቃድ ቪዛ ውድቅ ተደርጎባቸው የነበረ ቢኾንም አሁን ግን በዓለም አቀፍ ዳኝነት ሥራቸው ትልቅ የተባለ ታሪካዊ ዕድል ገጥሟቸዋል።
እንደ ስካይ ስፖርት ዘገባ ነሀሴ 6/2018 ዓ.ም በሚካሄደው በዚህ ታላቅ መርሐ ግብር ዑመር አርታን ጨዋታውን በመምራት በአውሮፓ ሱፐር ካፕ ታሪክ የመጀመሪያው አፍሪካዊ እና አውሮፓዊ ያልኾኑ ዳኛ በመኾን ስማቸውን በታሪክ ያሰፍራሉ።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here