ባሕር ዳር: ሚያዝያ 12/2018 (አሚኮ) በኢትዮጵያ ፕሪምዬር ሊግ 28ኛ ሳምንት ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ።
ባሕር ዳር ከተማ ከሸገር ከተማ የሚያደርገው ጨዋታ ከእነዚህ ጨዋታዎች መካከል አንዱ ነው። ይህ ጨዋታ በአዲስ አበባ አበበ ቢቄላ ስታዲየም ቀን 7፡00 ላይ ይካሄዳል።
በሌሎች ጨዋታዎች ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ መድን በአበበ ቢቄላ ስታዲየም እና ምድረ ገነት ሽረ ከወላይታ ዲቻ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተመሳሳይ ቀን 10፡00 ላይ ይጫዎታሉ።
የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !



