ባሕር ዳር: መጋቢት 25/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የአርሰናሉ አሠልጣኝ ሚኬል አርቴታ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጋቢት ወር ምርጥ አሠልጣኝ ተብለው ተመርጠዋል።
አሠልጣኝ ሚኬል አርቴታ አርሰናል በመጋቢት ወር ያደረጋቸውን የሊግ ጨዋታዎች ሁሉንም በድል እንዲወጣ ማድረጋቸውን ያሁ ስፖርት ዘግቧል።
አሠልጣኙ አርሰናልን ለእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ እያቀረቡት መኾኑንም ገልጿል። አሠልጣኙ በወሩ ሦስት የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን አድርገው ሦስቱንም አሸንፈዋል።
አርሰናል ከተከታዩ ማንቸስተር ሲቲ በዘጠኝ ነጥቦች ርቆ ሊጉን እየመራ ነው።
የኒውካስትል ዩናይትዱ አጥቂ ዊሊያም ኦሱላ ማንቸስተር ዩናይትድ ላይ ያስቆጠራት ግብ የመጋቢት ወር የወሩ ምርጥ ግብ ኾና ተመርጣለች።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!



