አርሰናል ቸልሲን በማሸነፍ ለሊግ ካፕ ፍጻሜ ደረሰ።

0
21
ባሕር ዳር፡ ጥር 26/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በእንግሊዝ ሊግ ካፕ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ አርሰናል እና ቼልሲ ያደረጉት ጨዋታ በአርሰናል አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
አርሰናል ቸልሲል 1ለ0 ማሸነፍ ችሏል።
የአርሰናልን የማሸነፊያ ግብ ሀቨርትዝ አስቆጥሯል።
አርሰናል ከሁለት ሳምንት በፊትም በስታምፎርድ ብሪጅ የነበረውን የመጀመርያ ዙር ጨዋታ 3ለ2 ማሸነፉ የሚታወስ ሲኾን በአጠቃላይ ውጤት 4ለ2 በኾነ ውጤት ለፍጻሜው ጨዋታ መድረሱን አረጋግጧል።
የሊግ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታው በግዙፉ የዌይምብሌ ስታዲየም የሚደረግ ይኾናል። አርሰናልም ለዚህ ፍጻሜ ጨዋታ ከማንቸስተር ሲቲ እና ኒውካስትል ዩናይትድ አሸናፊ ጋር የሚጫዎት ይኾናል፡፡
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!መ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here