አጫጭር የዝውውር ዜናዎች

0
52
👇
የተጫዋቾች ዝውውር ጥር 1/2026 ተጀምሮ የካቲት 2/ 2026 ደግሞ ይጠናቀቃል።
የዝውውር የጊዜው ከመቋጨቱ በፊት ዛሬን ጨምሮ ባሉት ሦስት ቀናት ቡድኖች ተጫዋቾችን ለማዘዋወር እየሰሩ ይገኛሉ። ከእነዚም መካከል፦
✍️ ቼልሲ የ22 ዓመቱን እንግሊዛዊ የሪያል ማድሪድ አማካይ ቤሊንግሃምን ለማስፈረም 150 ሚሊዮን ዩሮ ለማውጣት ማቀዱን ያስነበበው ፊቻጄስ ኢን ስፓኒሽ ነው።
✍️ ማንቸስተር ዩናይትድ ኮል ፓልመርን በዚህ የዝውውር ወቅት እንደማያስፈረም ሚረር አስነብቧል።
✍️ አያክስ አምስተርዳም አርሰናል ለኖቲንግሃም ፎረስት በውሰት ሰጥቶት እየተጫወተ የሚገኘውን የ29 ዓመቱን ዩክሬናዊ አማካኝ ኦሌክሳንደር ዚንቼንኮ በ1ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ በቋሚ ውል ለማስፈረም መዘጋጀቱን ፋብሪዚዮ ሮማኖ ነው የዘገበው።
✍️ ሪያል ማድሪድ ከሚፈልጋቸው አሰልጣኞች አንዱ የአስቶን ቪላው ኡናይ ኤምሪ መኾኑን ስካይ ስፖርት አስነብቧል።
✍️ ቼልሲ የ20 ዓመቱን ፈረንሳዊ የመሐል ክፍል ተከላካይ ጄረሚ ዣኬትን ለማስፈረም ከሬኔስ ቡድን ጋር ድርድር ላይ መኾኑን የዘገበው ጊቭሚስፖርት ነው።
✍️ ሪያል ማድሪድ የ26 ዓመቱን የማንቸስተር ዩናይትድ የመስመር ተከላካይ ዲዮጎ ዳሎትን ማስፈረም መፈለጉን ያስነበበው ፊቻጄስ ኢን ስፓኒሽ ነው።
✍️ ራሂም ስተርሊንግን ለማስፈረም ቶትንሃም በጥብቅ መፈለጉን ቲም ቶክ አስነብቧል። ዩቬንቱስ እና በርንለይም የተጫዋቹ ፈላጊዎች ናቸው።
በሙሉጌታ ሙጨ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here