ባሕር ዳር፡ ጥር 12/2018ዓ.ም (አሚኮ) በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አርሰናል ከኢንተር ሚላን ጋር ባደረጉት ጨዋታ ብራዚላዊው አጥቂ ገብርኤል ጂሰስ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ቡድኑ እንዲያሸንፍ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ለዚህም ድንቅ ብቃቱ የጨዋታው ኮከብ ተብሎ ተመርጧል።
ቪኒሺየስ ጁኒየር ደግሞ ሪያል ማድሪድ ከሞናኮ ጋር ባደረጉት ጨዋታ ብራዚላዊው ኮከብ ቪኒሺየስ ጁኒየር 1 ግብ በማስቆጠር እና 2 ለግብ የሚኾኑ ኳሶችን በማመቻቸት ድንቅ ብቃቱን አሳይቷል። በዚህም የጨዋታው ኮከብ በመኾን ተመርጦ ሽልማቱን ተቀብሏል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!



