ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 21/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ናይጄሪያ ዩጋንዳን 3ለ1 አሸንፋለች፡፡ ውጤቱን ተከትሎ ሦስቱንም ጨዋታ በማሸነፍ ናይጄሪያ በዘጠኝ ነጥብ ጥሎ ማፉን ተቀላቅላለች።
በዚሁ ምድብ ታንዛኒያ ከቱኒዚያ ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ ተጠናቅቋል።
ጨዋታው አቻ ቢጠናቀቅም ከዚህ በፊት በምድቡ አንድ ጊዜ ያሸነፈችው ቱኒዚያ ነጥቧን 4 በማድረስ ከምድቡ ሁለተኛ ኾና ጥሎ ማለፉን ተቀላቅላለች፡፡
በዚሁ ምድብ ዩጋንዳ እና ታንዛኒያ ወደ ሀገራቸው ተሸኝተዋል፡፡
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!



