ባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 21/2018 ዓ.ም ((አሚኮ) በሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 12ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ሲዳማ ቡና መሪነቱን የተረከበበትን ድል አስመዝግቧል።
ምሽት 12:00 በተጀመረው የሲዳማ ቡና እና የሸገር ከተማ ጨዋታ በሲዳማ ቡና 2ለ0 አሸናፊነት ተጠናቋል።
ግቦችንም 52 ደቂቃ ላይ ፍቅረየሱስ ተክለብርሀን እና
በ79ኛው ደቂቃ መስፍን ታፈሰ አስቆጥረዋል።
ውጤቱን ተከትሎ ሲዳማ ቡና በ25 ነጥብ የሊጉ መሪ ኾኗል።
በሙሉጌታ ሙጨ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!



