ፖርቹጋል 20ኛውን ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ውድድር አሸነፈች።

0
39
ባሕር ዳር: ኅዳር 17/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በኳታር አስተናጋጅነት ሲካሄድ በቆየው ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ውድድር ፖርቹጋል አሸናፊ ኾናለች።
ከኦስትሪያን ጋር ለፍጻሜ የተገናኘችው ፖርቹጋል 1 ለ 0 በኾነ ጠባብ ውጤት በማሸነፍ ሻምፒዮን ኾናለች።
በካሊፋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አኒሲዮ ባስቆጠራት ብቸኛ ግብ ፖርቹጋል አሸንፋ ዋንጫ አንስታለች።
48 ሀገራት በተሳተፉት እና ለ20ኛ ጊዜ በተደረገው ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ውድድር ፖርቹጋል በታሪኳ ለመጀመርያ ጊዜ ሻምፒዮን ኾናለች፡፡
ጣሊያን ብራዚልን በመለያ ምት በማሸነፍ ሦስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here