ባሕር ዳር: ግንቦት 26/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ( ዋሊያ) ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ከጊኒ ቢሳው ጋር ላለበት ጨዋታ ዛሬ ማለዳ ወደ ስፍራው አቅንቷል። ምሽት ላይም በሀገሪቱ መዲና ቢሳው ከተማ በሠላም ደርሷል። ጨዋታውም ሐሙስ ዕለት ይካሄዳል ሲል የኢትዮጵያ እግር ኳስፌዴሬሽን በድረ ገጹ አስነብቧል።
የጊኒ ቢሳው የሕዝብ ቁጥር 2 ነጥብ 1ሚሊዮን ሲኾን ብሔራዊ ቡድኗ በፕሮፌሽናል ተጫዋቾች የተዋቀረ መኾኑን ቢሳው ታይምስ ዘግቧል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!