አጫጭር የዝውውር ዜናዎች ከአሚኮ፦

0
68
ባሕር ዳር: ነሐሴ 23/2017 ዓ.ም (አሚኮ)
👉ኮቢ ማይኑ በውሰት ዩናይትድን ለመልቀቅ ጥያቄ አቅርቧል። ነገር ግን ዩናይትድ የተጫዋቹን ጥያቄ ውድቅ ማድረጉን ጎል ጽፏል። አሠልጣኝ አሞሪም ማይኑን እንፈልገዋለን ብለዋል።
👉በቢቢሲ መረጃ መሠረት ዣቪ ሲሞንስ ወደ ቶትንሃም የሚያደርገውን ዝውውር ለማጠናቀቅ የሕክምና ምርመራውን አጠናቅቋል።
👉ሊቨርፑል ለኢሳክ ዝውውር 130ሚሊዮን ፓውንድ ለማቅረብ መዘጋጀቱን ቴሌግራፍ አስነብቧል። የተጫዋቹ ዝውውር በቀጣዮቹ 48 ሰዓታት መልክ እንደሚይዝም ዘገባው ጨምሯል።
👉አሠልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ ከፌነርባቼ አሠልጣኝነት ተሰናብተዋል። ፌነርባቼ ለሻምፒዮንስ ሊግ ማለፍ አለመቻሉ በአሠልጣኙ ስንብት ምክንያት መኾኑን ቢቢሲ በስፖርት ገጹ አስነብቧል።
👉ቼልሲ ጋርናቾን ለማስፈረም ተስማምቷል። ተጫዋቹ በቀጣዮቹ ሰባት ዓመታት ለቼልሲ ለመጫወት ፊርማውን እንደሚያሰፍር ሜትሮ አስነብቧል።
👉ኒውካስትል ዩናይትድ ከጀርመኑ ስቱትጋርት አጥቂ ለማስፈረም ጫፍ ደርሷል። ኒክ ዋልቲሜድ የተሰኘው ይህ ተጫዋች በባየር ሙኒክ ሲፈለግ ነበር ብሏል ስካይ ስፖርት።
👉አርሰናል የፒሮ ሂንካፒን ዝውውር ለማጠናቀቅ ተቃርቧል። አርሰናል ተጫዋቹን በውስት ለማስፈረም እና በቀጣይ ተጫዋቹን በቋሚነት ከፈለገ 60 ሚሊዮን ዩሮ ለመክፈል ከሊቨርኩሰን ጋር ተስማምቷል።
👉ጎል አርሰናል እና ፖርቶ በኪዌር ዝውውር ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስነብቧል። ተከላካዩ በአርቴታ ተመራጭ ባለመኾኑ ነው አርሰናልን የሚለቀው።
👉ሪያል ማድሪድ ኦፕሚካኖን በቅርበት እየተከታታለ ነው ሲል የዘገበው ደግሞ ስፖርት ቢልድ ነው። ተጫዋቹ የባየር ሙኒክ ውሉ በቀጣይ ዓመት የሚጠናቀቅ ይኾናል። ለተጨማሪ ጊዜ ለመቆየት እስካሁን ስምምነት ላይ አልደረሰም።
👉የቱርኩ ቢሽክታሽ ኦሊጎኖ ሾልሻየርን ከአሠልጣኝነት አንስቷል። ቢሽክታሽ በኮንፈረንስ ሊግ በቀድመ ጨዋታ በመሸነፉ ነው የቀድሞው የዩናይትድ ተጫዋች እና አሠልጣኝ ለስንብት የተዳረገው።
ዘጋቢ፦አስማማው አማረ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here