ኢንተር ሚላንን ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ያበቁት ሲሞኒ ኢንዛጊ ወደ ሳኡዲ ሊግ ለማምራት ተስማምተዋል። አሠልጣኙ አል ሂላልን ለማሠልጠን ነው የተስማሙት። የሦስት ዓመት ውል የሚፈርሙም ይኾናል።
ጣሊያናዊ አሠልጣኝ በኢንተር ስኬታማ ጊዜ ነበራቸው። በአራት ዓመት ቆይታቸው አንድ የሴሪ ኤ፣ ሁለት ኮፖ ኢታሊያ እና ሦስት የሱፐር ካፕ ድሎችን አጣጥመዋል።
በአራት ዓመት ውስጥ ክለቡን በሁለት አጋጣሚ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ አድርሰውታል።