ሀዋሳ ከተማ እና ኢትዮጵያ መድን ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል።

0
155

ባሕር ዳር:ሚያዝያ 14/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ዛሬ በተደረጉ የኢትዮጵያ ፕሪምዬር ሊግ ጨዋታዎች ሀዋሳ ከተማ እና ኢትዮጵያ መድን ድል ቀንቷቸዋል።

ኢትዮጵያ መድን ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2ለ0 በማሸነፍ ነው መሪነቱን ያጠናከረው። ሁለቱንም የማሸነፊያ ግቦች መሐመድ አበራ አስቆጥሯል።

ሀዋሳ ከተማ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያደረጉት ጨዋታ ደግሞ በሀዋሳ ከተማ 2ለ1 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።

የሀዋሳ ከተማን የማሸነፊያ ሁለት ግቦች አሊ ሱሌማን ሲያስቆጥር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ከሽንፈት ያልታደገች ግብ ሱሌማን ሀሚድ አስቆጥሯል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here