በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ውድድሮች ኢትዮጵያ በሦስት ውድድሮች ተጋጣሚዎቿን ለየች።

0
144

ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 03/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የተለያዩ የሴቶች ውድድሮች የዕጣ ማውጣት ሥነ ሥርዓት አከናውኗል። በዚህም ኢትዮጵያ በሦስት ውድድሮች ተጋጣሚዎቿን ለይታለች። የ2026 የአፍሪካ ሴቶች ዋንጫ ማጣሪያ አንደኛ ዙር ዩጋንዳን ከኢትዮጵያ ያገናኛል።

የ2026 የአፍሪካ ዞን የሴቶች ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣርያ ሁለተኛ ዙር ላይ ኢትዮጵያ ከኬንያ ትገናኛለች።

የ2025 የአፍሪካ ዞን የሴቶች ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ አንደኛ ዙር ላይ ዚምባብዌ ከኢትዮጵያ ይገናኛሉ።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here