የ2016 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ በወላይታ ድቻ እና ኢትዮጵያ ቡና መካከል ሰኔ 30 ይካሄዳል።

0
244

ባሕር ዳር: ግንቦት 22/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮጵያ ቡና ከወላይታ ድቻ የሚያደርጉት የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ሰኔ 30/2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚከናወን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ጨዋታው የሚካሄድበት ስታዲየም በቀጣይ ይፋ እንደሚደረግም ከፌዴሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ኢትዮጵያ ቡና ሀዋሳ ከተማን እንዲሁም ወላይታ ድቻ ኢትዮጵያ መድንን በግማሽ ፍጻሜው በማሸነፍ ለፍጻሜ ማለፋቸው ይታወቃል። የውድድሩ አሸናፊ ኢትዮጵያን ወክሎ በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ይሳተፋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here