ኢትዮጵያ በ10 ሺህ ሜትር ወንዶች አራተኛ ወርቅ አገኘች።

0
325

ባሕር ዳር: መጋቢት 10/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በጋና እየተከናወነ በሚገኘው 13ኛው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ 4ኛውን የወርቅ ሜዳልያ እና 3ኛውን የብር ሜዳልያ በወንዶች 10 ሺህ ሜትር አስመዝግባለች።

በውድድሩ አትሌት ንብረት መላክ በ29:45.37 በቀዳሚነት ውድድሩን አጠናቅቋል። አትሌት ገመቹ ዲዳ በ29:45.68 የሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ወድድሩን ፈፅሟል። ኬንያዊው ኢቫንስ ኪፕቱም በ29:47.61 በሦስተኛነት ውድድሩን ጨርሶ የነሀስ ሜዳሊያ አግኝቷል። ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ኃይለማርያም አማረ 29:57.39 የሰባተኛ ደረጃን በመያዝ ወድድሩን ፈፅሟል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here