አትሌት ፎቴን ተስፋይ ለመጀመሪያ ጊዜ ባደረገችው የማራቶን ውድድሯ አሸነፈች።

0
55

 

ባሕር ዳር: መጋቢት 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ)በዓለም አትሌቲክስ የነሐስ ደረጃ በተሰጠው የባርሴሎና ማራቶን አትሌት ፎቴን ተስፋይ በመጀመሪያ የማራቶን ውድድሯ በታሪክ ሁለተኛውን የዓለም ፈጣን ሰአት በማስመዝገብ አሸንፋለች።

አትሌት ፎቴን ውድድሩን ለማጠናቀቅ 2 ሰዓት 10 ደቂቃ 53 ሴኮንድ ወስዶባታል። አትሌት ፎቴን የቦታውን ክብረወሰን በመስበር ነው ማሸነፍ የቻለችው ።

በውድድሩ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አትሌት ዘይነባ ይመር ሦሥተኛ ፣አትሌት ጫልቱ ጬምዴሳ አራተኛ እና አትሌት ያልጋነሽ እስከመች አምስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን ማጠናቀቃቸውን ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here