የፕሪሚየር ሊግ ቡድኖች ዛሬ ይፈተኑ ይኾን?

0
55
ባሕር ዳር: 08/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ዋንጫ አራተኛ ዙር ዛሬ አምስት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ።
በጨዋታዎቹ የፕሪሚየር ሊግ ቡድኖች በታችኛው ዲቪዚዮን ቡድኖች ከመፈተን ባለፈ ነጥብ ሊጥሉ ይችላሉ ሲል ዴይሊ ስፖርት አስነብቧል።
ምሽት 1:30 ላይ የፕሪሚየር ሊጉ መሪ አርሰናል በሊግ አንድ ከሚሳተፈው ዊጋን አትሌቲክ ጋር በኤሚሬትስ ስታዲየም ይጫወታል።
ሁለቱ ቡድኖች በኤፍ ኤ ዋንጫ ታሪክ በአንድ ጨዋታ ተገናኝተው በአቻ ውጤት ነው የተለያዩት። ዛሬስ? ምሽት 1:30 ላይ የሚደረገው ጨዋታ ምላሹን ይሰጣል።
አሠልጣኝ አርቴታ ለጨዋታው እንደማንኛውም ጨዋታ ትኩረት ሰጥተን ቋሚ ተሰላፊዎችን እንጠቀማለን ብለዋል።
ከብሬንትፎርድ የአቻ ውጤት በኋላም ዛሬ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ እንጫወታለን ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በሌሎች ጨዋታዎች
👉 ቀን 9:00 ላይ በርሚንግሃም ከሊድስ ዩናይትድ
👉 ቀን 10:30 ላይ ግሪምስባይ ከዎልቭስ
👉 ቀን 11:00 ላይ ኦክስፎርድ ከሰንደርላንድ
👉 በተመሳሳይ ቀን 11:00 ላይ ስቶክ ሲቲ ከፉልሃም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በሙሉጌታ ሙጨ
አሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here