የጥር ወር የተጫዋቾች ዝውውር ለእንግሊዝ ቡድኖች በይፋ መዘጋቱን ቢቢሲ ዘግቧል። የተለያዩ ቡድኖችም ያስፈረሟቸውን እያሳወቁ ነው። መዚህም መሠረት፦
👉 ሼፍ ዩናይትድ የማንቸስተር ሲቲውን አማካይ ካልቪን ፊሊፕስን በውሰት ውል አስፈርሟል።
👉 ክሪስታል ፓላስ ስትራንድ ላርሰንን በ48 ሚሊዮን ፓውንድ ከወልቭስ ማስፈረሙን አሳውቋል።
👉 ሴልቲክ ኦስትሪያዊውን አጥቂ ጁኒየር አዳሙን ከጀርመኑ ፍሬይበርግ ቡድን ላይ በውሰት ውል አስፈርሟል።
የ24 ዓመቱ ተጫዋቹ የተወለደው ናይጄሪያ ውስጥ ነው።
👉 ቶትንሃም የ18 ዓመቱን የሃርትስ አጥቂ ጀምስ ዊልሰንን በውሰት ውል አስፈርሟል።
👉 ፊዮሬንቲና ዳኒኤል ሩጋኒን ከጁቬንቱስ ላይ በዉሰት ውል ማስፈረሙን ኢታሊያን ኢን ፔፐር አስነብቧል።
👉 ሰንደርላንድ ከኢኳዶራዊው የአንደርሌክት ተጫዋች ኒልሰን አንጉሎን ጋር በ17 ነጥብ 5 ሚሊዮን ፓውንድ ውል አስፈርሟል።
👉 አትሌቲኮ ማድሪድ የ28 ዓመቱ ናይጄሪያዊ አድሞላ ሉክማንን ለማስፈረም በመርሕ ደረጃ ተስምቷል።
👉 ጁቬንቱስ ኤሚል ኾልምን ከቦሎኛ በውሰት ዉል ማግኘቱ ተረጋግጧል።
በሙሉጌታ ሙጨ



