ባሕር ዳር፡ ጥር 23/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ 24ኛ ሳምንት ጨዋታ አርሰናል ሊድስ ዩናይትድን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል።
አርሰናል ሊድስ ዩናይትድን ማሸነፍ የቻለው 4ለ0 በኾነ ውጤት ነው።
የአርሰናልን የማሸነፊያ ግቦች ዙበሜንዲ፣ ዮኬሬሽ፣ጀሰስ እና ዳርሎ በራሱ መረብ ላይ አስቆጥረዋል።
በሌሎች የሊጉ ጨዋታ ቦርንማውዝ ወልቨስን 2ለ 0 ሲያሸንፍ ኤቨርተን ከብራይተን አቻ ተለያይተዋል።
ሊጉን አርሰናል በ53 ነጥብ ሲመራ ሲቲ 46 ይከተላል አስቶንቪላ ደግሞ በግብ ክፍያ ተበልጦ ሦሥተኛ ጀረጃ ላይ ይገኛል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!



