ባሕር ዳር: ጥር 06/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ሴኔጋልን ከግብጽ ጋር አገናኝቶ ሴኔጋል አሸንፋ ለዋንጫ ጨዋታው ደርሳለች።
ሴኔጋል ግብጽን ያሸነፈችው 1ለ0 በኾነ ውጤት ነው።
የሴኔጋልን የማሸነፊያ ግብ ሳድዮ ማኔ አስቆጥሯል።
ሴኔጋል ለዋንጫ ጨዋታውም ከአዘጋጇ ሞሮኮ እና ናይጀሪያ አሸናፊ ጋር የምትገናኝ ይኾናል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!



