
ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 25/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በ20ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ቦርን ማውዝን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል።
አርሰናል ቦርንማውዝን ያሸነፈው 3ለ2 በኾነ ውጤት ነው።
የአርሰናልን የማሸነፊያ ግቦች ሁለቱን ራይስ ሲያስቆጥር አንዷን ግብ ገብሬል ማጋሌሽ አስቆጥሯል።
የቦርንማውዝን ግቦች ኤቫኒልሰን እና ክሮፕ አስቆጥረዋል።
በሌላ የሊጉ ጨዋታ ዎልቭስ ዌስትሀም ዩናይትድን 3ለ0 በማሸነፍ የመጀመርያ ድሉን አግኝቷል፡፡
ብራይተን ደግሞ በርንሌይን 2ለ0 አሸንፏል፡፡
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!


