ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 25/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ስመ ጥር የዓለማችን የእግር ኳስ ቡድኖች በጥር ወር የተጫዋቾች የዝውውር ገበያ በንቃት እና በስፋት እየተሳተፉ እንደሚገኙ ቢቢሲ የተለያዩ የመረጃ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።

የሪያል ማድሪዱ የክንፍ መስመር ተጫዋች ሮድሪጎ በአርሰናል፣ በማንቸስተር ሲቲ እና በሊቨርፑል እየተፈለገ የሚገኝ ተጫዋች መኾኑን አስ – ስፓኒሽ አስነብቧል።

ማንቸስተር ዩናይትድ የብራይተኑን ካሜሩናዊ የ21 ዓመት ካርሎስ ባሌባን ለማስፈረም ፍላጎት አሳይቷል ያለው ስካይ ስፖርት ነው።

ዌስትሃም ዩናይትድ የ27 ዓመቱን አጥቂ ታቲ ካስቴላኖስን በ25 ሚሊዮን ፓውንድ ለማስፈረም ትኩረት አድርጓል።

ሊቨርፑል፣ ማንቸስተር ዩናይትድ እና ኒውካስትል የዋትፎርዱን ሞሮኳዊ የፊት መስመር አጥቂ ኦዝማኔ ማዓማዓ ላይ ዐይናቸውን ጥለውበታል።

ክሪስታል ፓላስ፣ ሊድስ ዩናይትድ እና ኖቲንግሃም ፎረስት የ26 ዓመቱ እንግሊዛዊ አማካኝ ጆ ዊሎክን ለማስፈረም ፉክክር ውስጥ ገብተዋል።

ፉልሃም የ22 ዓመቱን አሜሪካዊ አጥቂ ሪካርዶ ፔፒን ከፒኤስቪ ለማስፈረም ያደረጉት ጥረት ሳንካ ገጥሞታል ሲል ዘ ሰን አስነብቧል።