የአፍሪካ ዋንጫ ዛሬ ይጀምራል።

0
3
ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 12/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የ2025ቱ የአፍሪካ ዋንጫ በሞሮኮ አስተናጋጅነት ዛሬ ይጀምራል። ሞሮኮ ኮሞርስን የምትገጥምበት ጨዋታም የውድድሩ የመክፈቻ ጨዋታ ነው።
ስለ አፍሪካ ዋንጫው ከታሪክ በትቂቱ👇
✍️አዘጋጇ ሞሮኮ ዋንጫውን ለማንሳት ቅድመ ግምት በማግኘት ቁጥር አንድ ላይ መቀመጧን አልጀዚራ አስነብቧል። ኮትዲቫር፣ ሰኔጋል እና ግብጽም ዋንጫ የማንሳት ቅድመ ግምት ያገኙ ሀገራት ናቸው።
✍️ኮትዲቯር የ2023ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት ናት
✍️ሞሮኮ ለውድድሩ በስድስት ከተሞች የሚገኙ ዘጠኝ ስታዲየሞችን አዘጋጅታለች። ይህም በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ ብዙ ሜዳዎች ጨዋታ የሚያስተናግዱበት የአፍሪካ ዋንጫ ያደርገዋል።
✍️ካፍ የ2025ቱን የአፍሪካ ዋንጫ እንድታዘጋጅ መጀመሪያ ለጊኒ እድል ሰጥቶ የነበረ ቢኾን በኋላ ላይ በሀገሪቱ የአዘጋጅነት ላይ እምነት በማጣቱ እድሉን ነጥቆ ለሞሮኮ ሰጥቷል።
✍️ግብጽ የአፍሪካ ዋንጫን ሰባት ጊዜ በማንሳት ቀዳሚዋ ሀገር ናት።
✍️ሞሮኮ የአፍሪካ ዋንጫን ስታዘጋጅ ይህ ሁለተኛዋ ሲኾን ከዚህ በፊት እ.ኤ.አ 1988 አዘጋጅታ ነበር።
👇አዘጋጇ ሞሮኮ የአፍሪካ ዋንጫን ያሸነፈችው በታሪክ አንድ ጊዜ ሲሆን ጊዜው እንደአውሮፓውያን አቆጣጠር 1976 ኢትዮጵያ ባዘጋጀችው ድግስ ነበር።
✍️የዘንድሮውን ዋንጫ የሚያነሳ ሀገር 7 ሚሊዮን ዶላር የሚሸለም ሲኾን ሁለተኛ ደረጃን ይዞ የሚያጠናቅቀው ደግሞ 4 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ይበረከትለታል።
✍️እነዚህን ሽልማቶች ጨምሮ ካፍ 32 ሚሊዮን ዶላር ለዚህ ውድድር ለሽልማት አዘጋጅቷል።
✍️የአፍሪካ ዋንጫ በሦስት ሀገራት የተጀመረ ሲሆን አሁን ላይ 24 ሀገራት የማጣሪያ ጨዋታቸውን አልፈው ሞሮኮ ላይ ለመድመቅ ውድድሩን እየተጠባበቁ ነው።
በሰመሀል ፍስሀ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here