ባሕር ዳር: ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በፕርሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቶተንሀም ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2 ለ 2 በኾነ አቻ ውጤት አጠናቅቀዋል።
የቶተንሀምን ግቦች ማትያስ ቴል እና ሪቻርልሰን ማስቆጠር ችለዋል።
ለማንችስተር ዩናይትድ ብሪያን ምቤሞ እና ማትያስ ዴሊት አስቆጥረዋል።
በደረጃ ሰንጠረዡን ቶተንሀም በ18 ነጥብ ሦስተኛ እና ማንችስተር ዩናይትድ በ18 ነጥብ ሰባተኛ ላይ ተቀምጠዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!



