ማንቸስተር ሲቲ ጃንሉጂ ዶናሩማን ለማስፈረም ተስማማ።

0
133
 ባሕር ዳር: ነሐሴ 26/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ማንቸስተር ሲቲ ጣልያንዊውን ግብ ጠባቂ ጃንሉጂ ዶናሩማን ለማስፈረም ተስማምቷል።
ከፈረንሳዩ ክለብ ፒኤሰጂ ጋር እንደማይቀጥል የተነገረው ዶናሩማ ስሙ ከተለያዩ ክለቦች ጋር ሲያያዝ ቆይቷል። በመጨረሻም ለማንቸስተር ሲቲ ለመጫወት መስማማቱን ፋብሪዚዮ ሮማኖ አስነብቧል። ሊጠናቀቅ በተቃረበው የዝውውር ወቅት በርከት ያሉ ዝውውሮች እየተፈጸሙ ነው። ማንቸስተር ዩናይትድ አንቶኒን ለሪያል ቤቲስ ለመሸጥ ተስማምቷል። ጁቬንቱስ ደግሞ አጥቂውን ሎኢስ ኦፔንዳን ከአሪ ቢ ሊብዚንግ ለማስፈረም መስማማቱ ተገልጿል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here