ባሕር ዳር: ነሐሴ 15/2017 ዓ.ም (አሚኮ) 30 ኛውን የአሚኮ የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የሚዲያዎች እግር ኳስ ካፕ መካሄድ ጀምሯል።
በመክፈቻ መርሐ ግብሩ የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ጋዜጠኛ ሙሉቀን ሰጥየ ተገኝተው ውድድሩን አስጀምረዋል። በውድድሩ የመክፈቻ መርሐ ግብር አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ተገናኝተዋል። በአሚኮ ካፕ የእግር ኳስ ውድድር አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽንን ጨምሮ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ እና ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደሚሳተፉ ለማወቅ ተችሏል።
ዘጋቢ፦ አሰፋ ልጥገበው
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!