ቼልሲ የፊፋ ክለቦች ዓለም ዋንጫን አነሳ።

0
80

ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 07/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ቼልሲ የፊፋ የክለቦች ዓለም ዋንጫን ፍጻሜ ጨዋታ ላይ ፓሪስ ሴንት ዠርሜንን በፍጹም የጨዋታ የበላይነት አሸንፎ ዋንጫውን አንስቷል። ቸልሲ ፒ ኤስ ጅን 3 ለ 0 ነው በማሸነፍ ዋንጫውን ያነሳው።

የማሸነፊያ ግቧን ኮል ፓልመር በ22ኛው እና በ30ኛው ደቂቃ ሲያስቆጥር አዲሱ የሰማያዊዎቹ ፈራሚ ጆአዎ ፔድሮ በ43ኛው ደቂቃ ላይ ሦስተኛውን ግብ አስቆጥሯል።

በሁለተኛው አጋማሽ ፒኤስ ጅ የግብ ክፍተቱን ለማጥበብ ጥረት ቢያደርግም አልተሳካለትም።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here