ተቋርጦ የነበረው የመላው ኢትዮጵያ ጨዋታ ሊካሄድ ነው፡፡

0
106

ባሕር ዳር: ሰኔ 05/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ሁሉም ክልሎች እና ከተማ አሥተዳደሮች የሚሳተፉበት የመላው ኢትዮጵያ ጨዋታ በጅማ ከተማ እንደሚካሄድ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

በ6ኛው መላው ኢትዮጵያ ጨዋታ በ26 የስፖርት አይነቶች ከ4ሺህ 500 በላይ ስፖርተኞች ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡

የባሕልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ መክዩ መሐመድ ለሁለት ሳምንት የሚቆየው ውድድሩ ተተኪ ስፖርተኞችን ማፍራት ላይ ትኩረት ተደርጎ እነደሚካሄድ ተናግረዋል፡፡

ለውድድሩ በቂ ዝግጅት መደረጉንም ገልጸዋል፡፡ ውድድሩ ከሰኔ 10/2017 ዓ.ም እስከ ሰኔ 19/2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚካሄድ ተገልጿል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here