በሴቶች የዓለም ዋንጫ የቦክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያን በሁለት ቦክሰኞች ትወከላለች።

0
144

በሰርቢያንስ ከተማ በሚካሄደው የሴቶች የዓለም ዋንጫ የቦክስ ውድድር ላይ ኢትዮጵያን በመወከል የአዲስ አበባ ፖሊስ ሴት ቦክሰኞች ይሳተፋሉ።

ሮማን አሰፋ እና ሚሊዮን ጨፎ ናቸው ኢትዮጵያን የሚወክሉት። ከአሠልጣኞቻቸው ጋር ሽኝት ተደርጎላቸዋል።

በሽኝት መርሐ ግብሩ የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ የኮሚሽን ጨምሮ ሌሎች የፌደራል እና የክልል ፖሊስ ከፍተኛ መሪዎች ተገኝተዋል።

በሰርቢያንስ ከተማ የሚካሄደው የሴቶች የዓለም ዋንጫ የቦክስ ውድድር ከየካቲት 27/2017 ጀምሮ ለ11 ቀናት የሚቆይ ነው።

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here