በጃፓን ኦሳካ የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ድል ቀናቸው።

0
138

ባሕር ዳር: የካቲት 17/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በጃፓን ኦሳካ የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል።

በጃፓን ኦሳካ በተካሄደው የማራቶን ውድድር በሁለቱም ጾታ በኢትዮጵያውያን አትሌቶች የበላይነት ተጠናቅቀዋል።

👉በወንዶች ማራቶን ውድድር
አትሌት ይሁንልኝ አዳነ የቦታውን ሰዓት በማሻሻል እና የራሱን ምርጥ ሰዓት በማስመዝገብ በአንደኝነት አጠናቋል።

አትሌት ይሁንልኝ ርቀቱን 2:05:37 በኾነ ሰዓት በመግባት ነው ያሸፈው።

👉በሴቶች ማራቶን ውድድር
አትሌት ዋጋነሽ መካሻ 2:26:33 በኾነ ሰዓት በመግባት በቀዳሚነት አጠናቃለች ።

ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው በሜክሲኮ ጓዳላሀራ በተካሄደው ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ታዱ አባተ 62:02 በመግባት አሸንፏል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here